![](https://cdn.al-ain.com/images/2019/12/18/223-164026-whatsapp-image-2019-12-17-at-15.44.38-1-_700x400.jpeg)
ኢትዮጵያ የምታመጥቃት ETRSS-1 አነስተኛ የመሬት ምልከታ ሳተላይት የቁጥር መረጃ ምን ይመስላል? በቀጣዩ የኢንፎግራፊክ ምስል ላይ ይመልከቱ
በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የተባለችው ETRSS-1 አነስተኛ የመሬት ምልከታ ሳተላይት (Small Remote Sensing Satellite) በመጪው አርብ ማለዳ ወደ ህዋ እንደምትመጥቅ ተነግሯል፡፡
በቻይና መንግስት ድጋፍ በኢትዮጵያውያን የምህንድስና ጠበብቶች የተሰራችው ይህች ሳተላይት ከቤጂንግ 5 መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የቻይና ጠፈር ምርምር ማዕከል ነው ወደ ህዋ የምትመጥቀው፡፡