ሩሲያ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት መስማማቷ ይታወሳል
ዶላን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ፕሬዝደንት ፑቲን ተናግረዋል፡፡
ፕሬዝደንት ፑቱን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ንግግር ባሰሙበት ወቅት ሩሲያ ከምእራባውያን የተሰነዘሩባትን መእቀቦች መቋቋም መቻሏን መግጻቸውን የሩሲያው አርቲ ዘግቧል፡፡
ሩሲያ ማእቀቦቹን የተቋቋመችው የተለያዩ የመከላከያ መንገዶችን በመጠቀም ነው ብለዋል ፑቲን፡፡
በቀጣይ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች ላይ የተናገሩት ፑቲን ዶላርን ከመገበያያነት የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሩሲያ በዩክሬን ላይ “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ አሜሪካን ጨምሮ ምእራባውያን በሺዎች የሚቆጠሩ ማእቀቦችን ጥለውባታል፡፡ ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ከስምምነት መድረሷ ይታወሳል፡፡
ሩሲያ ምእራባውያን ለሚገዙት ጋዝ በሩሲያ ገንዘብ ሩብል እንከፍሉ በማድረግ እና ከዚህም አለፍ ሲል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዝጋት በምእራባውያን ሀገራት የአጸፋ እርምጃ ወስዳለች፡፡ በቅርቡ ለጥገና በሚል የዘጋችው ጋዝን ከሩሲያ ወደ ጀርመን የሚደውስደው ኖርድ ስትሪም 1 የተሰኘውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር እንደማትከፍት መግለጽ ይታወሳል፡፡
ጀርመን በሩሲያ ውሳኔ በእጅጉ አዝናለች፡፡
ሩሲያ እውቅና የሰጠቻቸው ሉሃንስክ ግዛት አሁን ሙሉበሙሉ ነጻ የወጣ ሲሆን የዶምባስ ግዛትን ሙሉ ለሙሉ ነጻ ለማውጣት ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡፡
ዩክሬን በቅርቡ በሩሲያ ሃይሎች ላይ ድል በመቀዳጀት የተወሰኑ ቦታዎች ማስለቀቋን እየገለጸች፤ ነገርግን ሩሲያ ቦታ የለቀቀችው ጦሯን በደንብ ለማደራጀት ነው ብላለች፡፡