ልዩልዩ
የብራዚል ፕሬዝዳንት ወረርሽኙን በያዙበት ሁኔታ ላይ በህግ ሊጠየቁ ነው
ትናንት ብቻ 4,200 የቫይረሱ ተጠቂዎች በሞቱባት ብራዚል እስካሁን የ345,000 ሰዎች ህይወት አልፏል
![](https://cdn.al-ain.com/images/2021/4/09/244-134339-9b602bf5-df0f-4fae-a7f5-b09f64efa4ef_700x400.jpg)
በቦልሶናሮ የወረርሽኝ አያያዝ ላይ ምርመራ እንዲደረግ የሃገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዟል
በብራዚል ፕሬዝዳንት ጃኤር ቦልሶናሮ እና በመንግስታቸው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አያያዝ ላይ ምርመራ እንዲደረግ የሃገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዘዘ፡፡
የሃገሪቱ ምክር ቤት ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ መንግስት እንዲመረመር ጠይቋል፡፡
ብራዚል በከፍተኛ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ቀዳሚወን ስፍራ ትይዛለች፡፡
በርካቶች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን እያጡ ይገኛሉም፡፡
ይህን ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች እንዲኖሩ በማሰብ በባለሙያዎች የቀረበውን ምክረ ሃሳብ ፕሬዝዳንቱ ውድቅ አድርገዋል፡፡
ምንም ዓይነት የእንቅስቃሴ ገደቦችን እንደማይጥሉም ነው ቦልሶናሮ ያስታወቁት፡፡
በዚህም ከ81ዱ የሃገሪቱ ምክር ቤት አባላት 32ቱ ፕሬዝዳንቱ እንዲመረመሩ ጠይቀዋል፡፡
የምክር ቤቱን ጥያቄ የተቀበለው የሃገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም መርማሪ ኮሚሽን እንዲቋቋም ፈቅዷል፡፡
ትናንት ብቻ 4,200 የቫይረሱ ተጠቂዎች በሞቱባት ብራዚል እስካሁን የ345,000 ሰዎች ህይወት በቫይረሱ ምክንያት ማለፉ ተረጋግጧል፡፡
በብራዚል እስካሁን 13.28 ሚሊዬን ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡