የፈተና መልሶችን ለማቀበል በገመድ ህንጻ የሚወጡት ህንዳውያን…
በሰሜናዊ ህንድ ሃርያና በተባለችው ግዛት ፊልም መሳይ የፈተና መልስ ማቀበል ሙከራ ተደርጓል
ትምህርት ቤቱ ግን “ፈተናው አልተሰረቀም፤ ተፈታኞቹ መልሱ እንዳይደርሳቸው ተደርጓል” ብሏል
የብሄራዊ ፈተናዎች ኩረጃና ማጭበርበር ፈተና በሆነባት ህንድ ከሰሞኑ አስገራሚ ክስተት ታይቷል።
የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና የሚወስዱበት ትምህርት ቤት በተፈታኞቹ ጓደኞች እና ወዳጆች ተወሯል።
በሰሜናዊ ህንድ ሃርያና ግዛት ኑህ በተባለችው ወረዳ የሚገኝ ቻንድራዋቲ የተባለ ትምህርት ቤት ነው ያልተጠበቀ ክስተት ያስተናገደው።
ኢንዲያን ታይምስ እንዳስነበበው አንድ ግለሰብ የሰውነት ማጎልመሻ ፈተናንን በፎቶ አንስቶ በመውጣት ለተፈታኝ ቤተሰቦች አቀብሏል።
ከዚያም የጥያቄዎቹ መልስ በፍጥነት ተሰርቶ የተፈታኞቹ ወዳጅ ጓደኞች የትምህርት ቤቱን ህንጻ በፍጥነት መውጣት የጀመሩት።
በማህበራዊ ሚዲያዎች የተጋራው ምስልም የፈተና መልስ አቀባዮቹ ህንጻውን በፍጥነት ሲወጡ አንዳንዶቹም ከላይ ሆነው በገመድ ከታች ያሉትን ሲጎትቱ ያሳያል።
የፈተና መልሶችን የያዙት ግለሰቦች መልሱ እንዲደርሳቸው የሚፈልጉትን ተማሪዎች በመስኮት ስማቸውን በመጥራት ለማቀበል ሲሞክሩም ታይቷል።
ቻንድራዋቲ የተባለው ትምህርት ቤት ግን ፈተናው ተሰርቆ እንዳልወጣና በህንጻው ላይ እንደ ሸረሪት የተንጠለጠሉትም በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው መልሶቹን ማቀበል አልቻሉም ብሏል።
በህንድ በተማሪዎች መጻኢ ትልቅ ትርጉም በሚሰጣቸው ብሄራዊ ፈተናዎች ወቅት ኩረጃ፣ ተመሳስሎ በመግባት ለሌላ ሰው መፈተን እና ፈተናን አስቀድሞ የመስረቅ ሙከራዎች ተደጋግመው ይታያሉ።
ከአንድ ወር በፊትም ሴት መስሎ (ቀሚስ ለብሶ፤ የአጅ አንባር አድርጎ፤ የሴቶች ቦርሳ ይዞና ከንፈሩንም ቀለም ተቀብቶ) ለፍቅረኛው ፈተና ለመፈተን የገባው ህንዳዊ በቁጥጥር መዋሉን መዘገባችን ይታወሳል።
በቅርቡም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እህቱን ለመርዳት ወደ ፈተና መስጫ ጣቢያ ፖሊስ መስሎ ያመራው ህንዳዊ በቁጥጥር ስር መዋሉን መዘገባችን አይዘነጋም።
aXA6IDMuMTM3LjE2MS4yMjIg
ejasoft island