አውሮፓ የሩሲያን ጥቃት ለመመከት ተጨማሪ 1000 የኑክሌር አረሮች ያስፈልጓታል ተባለ
ትራምፕ ለአውሮፓ የሰጡትን የደህንነት ዋስትና ያነሳሉ የሚለው ስጋት በማየሉ አውሮፓውያን ከአሜሪካ ነጻ ሆነው ራሳቸውን የሚከላከሉበትን ለመቀየስ እየተወያዩ ይገኛሉ

ተመራጩ የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርስ ትራምፕ የአውሮፓ እጣፈንታ ብዙም እንደማያስጨንቃቸውና አስተማማኝ የጸጥታ አጋር እንደማይሆኑ ተናግረዋል
አውሮፓ ቭላድሚር ፑቲን የሚሰነዝሩትን ጥቃት ለመከላከል ተጨማሪ 1000 የኑክሌር አረሮች እንደሚያስፈልጓት የጀርመን የፖለቲካ ሳይንቲስቶች አስጠነቀቁ።
በስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሁቨር ኢንስቲትዩሽን ቪዚቲንግ ፌሎው የሆነው ዶክተር ማክስሚላን ተርሃሌ ሩሲያ ለማስወንጨፍ ዝግጁ የሆኑ 1500 የረጅም ርቀት ሚሳይሎች ያሏት ሲሆን አውሮፓ ግን ጥቂት መቶዎች ብቻ ናቸው አሏት ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ለአውሮፓ የሰጡትን የደህንነት ዋስትና ያነሳሉ የሚለው ስጋት አውሮፓውያን ከአሜሪካ ነጻ ሆነው ራሳቸውን የሚከላከሉበትን መንገድ ለመቀየስ ውይይት እንዲጀምሩ አድርጓል።
ተመራጩ የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርስ ትራምፕ የአውሮፓ እጣፈንታ ብዙም እንደማያስጨንቃቸውና አስተማማኝ የጸጥታ አጋር እንደማይሆኑ አስተያየት ተሰጥተዋል።
የመሀል-ቀኝ ዘመም ክርሰቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪ አውሮፓ ከዋሽንግተን ነጻ ሆና ራሷን እንድትከላከል ፈረንሳይና ጀርመን የኑክሌር ትብብራቸውን ማስፋት እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
በጀርመን የአሜሪካ ኑክሌር ጦር መሳሪያዎች የሚገኙ ሲሆን በኔቶ ኑክሌር መከላከያ ይጠበቃሉ። ነገርግን ትራምፕ ከሩሲያ ጋር እየፈጠሩ ያለው ግንኙነት በበርሊን ተጨማሪ የደህንነት ዋስትና ጉዳይ ውይይት እንዲደረግ ምክንያት ሆኗል።
ፈረንሳይ የኑክሌር ኃይሏ የአውሮፓ መከላከያ ኃይል አካል እንዲሆን የምትፈልግ ሲሆን የዩናይትድ ኪንግደም(ብሪታንያ) የኑክሌር ፖሊሲ ግን ግልጽ አለመሆኑ ይነገራል።
የእንግሊዙ ጋዜጣ ቴሌግራፍ ፈረንሳይ ለሩሲያ ግልጽ መልእክት ለማስተላለፍ ኑክሌር የታጠቁ ተዋጊ ጄቶችን ወደ ጀርመን የመላክ ሀሳብ እንዳላት ይፋ አድርጓል። የፈረንሳይ መንግስት በኑክሌር ዙሪያ የያዘውን አቋ (ዶክትሪን) አለመቀየሩን ገልጿል።
በጀርመን ከፍተኛ ተደማጭነት ያላቸው ዶክተር ታርሃሌ ቀደም ሲል አውሮፓውያን 1500 የአሜሪካ የኑክሌር አረሮችን መግዛት ወይም መከራየት አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ትራምፕ የዩክሬኑን ጦርነትን ለማስቆም ከሩሲያ ጋር መነጋገራቸውን ተከትሎ የአውሮፓን ደህንነት የሚጎዳ ስምምነት እንዲደረስ ሊያደርጉ ይችላሉ በሚል ዩክሬንና የአውሮፓ አጋሮቿ ስጋት ገብቷቸዋል።