በውጤት መዋዠቅ ውስጥ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድ በነገው እለት በሜዳው ቶተንሀምን ያስተናግዳል
ሁለቱ ቡድኖች በአምስት ጨዋታዎች ያስመዘገቡት ውጤት ተመሳሳይ ነው
ሁለቱ ቡድኖች በአምስት ጨዋታዎች ያስመዘገቡት ውጤት ተመሳሳይ ነው
16ተኛ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች አርሰናል እና ቼልሲ ድል ቀንቷቸዋል።
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት ማንችስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልትራፎርድ የሰሜን ለንደኑን ክለብ ቶተንሀም ያስተናግዳል፡፡
የተረጋጋ አቋም ማሳየት የተሳነው ማንችስተር በውጤት ቀውስ ውስጥ ይገኛል። ይህን ተከትሎም ኔዘርላንዳዊው አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ በከፍተኛ ጫና ውስጥ ይገኛሉ፡፡
በ2024/25 የዝውውር መስኮት ንቁ ተሳትፎ ሲያደርግ የነበረው ቡድኑ በተከላካይ፣ በአማካይ እና አጥቂ ስፍራዎች የሚጫወቱ ተጫዋቾችን 182.5 ሚሊየን ፓውንድ በማውጣት ቢያስፈርምም የአቋም መዋዠቁን ሊቀርፍ አልቻለም፡፡
ባሳለፍነው አመት በሊጉ 8ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ዩናይትድ ዘንድሮ የተሻለ አቋም እንደሚያሳይ ቢጠበቅም ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች ሁለቱን አሸነፎ ፣ አንድ አቻ እና ሁለት ሽንፈቶችን በማስተናገድ በደረጃ ሰንጠረዡ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
በአውሮፓ ሊግ ጨዋታዎች ባሳለፍነው ሳምንት ከቲዌንቲ ጋር በአቻ ውጤት የተለያየ ሲሆን በነገው እለት ደግሞ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አምስት ጨዋታዎች ተመሳሳይ ውጤት ካስመዘገበው ቶተንሀም ጋር ይገጥማል፡፡
በግብ ክፍያ ተበላልጠው በደረጃ ሰንጠረዙ 10 እና 11ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ሁለቱ ቡድኖች በነገው እለት ደረጃቸውን ለማሻሻል ከባድ ፉክክር እንደሚያደርጉ የእንግሊዝ ጋዜጦች ዘግበዋል፡፡
በተከላካይ መስመር በርካታ ተጫዋቾቹ የተጎዱበት ዩናይትድ በነገው እለት አዲስ ፈራሚውን ሌኒ ዮሮን ጨምሮ ሉክ ሻው ፣ ቪክተር ሊንዶልፍ እና የታይሬል ማላሲያን አገልግሎት አያገኝም፡፡
በአውሮፓ ሊግ ጨዋታ ከጉዳት ወደ ሜዳ የተመለሰው ሜሰን ማውንት በተቀያሪ ስፍራ ላይ ይገኛል፡፡
በእሁዱ ጨዋታ 4-2-3-1 አሰላለፍን እንደሚከተሉ የሚጠበቁት ቀያይ ሰይጣኖቹ ቋሚ 11 አሰላለፍ ውስጥ ኦናና ፣ ማዝራዊ ፣ ዲላይት ፣ ማርቲኔዝ ፣ ዳሎት ፣ ማይኖ ፣ ኤርክሰን ፣ ራሽፈሮርድ ፣ ፈርናንዴዝ ፣ ጋርናቾ እና ሆሉንድን አካተው ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡
በነገው ጨዋታ የታክቲክ ለውጥ ያደረጉት የቶተንሀሙ አሰልጣኝ ፖስትኮግሎ 4-3-3 አሰላለፍን ሲከተሉ ዲያን ኩለሰቭኪን እና ጄምስ ማዲሰንን ወደ አማካይ ስፍራ በማምጣት የሚጫወቱ ይሆናል፡፡
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች አርሰናል ሌስተር ሲቲን 4ለ2 እንዲሁም ቼልሲ ብራይተንን በተመሳሳይ 4ለ2 ማሸነፍ ችለዋል።
በዚህም አርሰናል በ14 ፣ ቼልሲ በ13 ነጥብ በሊጉ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
በሌሎች ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ የቻለው ኤቨርተን የውድድር አመቱ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።
በተጨማሪም ፉልሀም ኖቲንገሀምን 1ለ0 ሲያሸንፍ ብሬንትፎርድ ከዌስትሀም ዩናይትድ 1ለ1 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል።