ተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በትግራይ ያለው ውጥረት እንዲረግብ ጠየቁ
ኮሚሽነር ባችሌት በትግራይና በኦሮሚያ ያለው የጸጥታ ችግር እንደሚያሳስባቸው ገልጸዋል
ኮሚሽነር ባችሌት በትግራይ ያለው ውጥረት እንዲረግብና ሁሉን አካታች የሆነ ንግግር እንዲያደርጉ ለሁሉም አካላት ጥሪ አቀረቡ
ኮሚሽነር ባችሌት በትግራይ ያለው ውጥረት እንዲረግብና ሁሉን አካታች የሆነ ንግግር እንዲያደርጉ ለሁሉም አካላት ጥሪ አቀረቡ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚቼል ባችሌት በትግራይ ያለው ውጥረት እንዲረግብና ሁሉን አካታች የሆነ ንግግር እንዲያደርጉ ለሁሉም አካላት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል መካከል ያለው አለመግባባት ባለፈው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ክልሉን የሚመራው ህወሓት በመከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ማድረሱንና እርምጃ እንደሚወስዱ ካሳወቁ በኋላ ወደ ግጭት አምርቷል፡፡
“ባለፋው ሳምንት አሳሰቢ የሆነ የጸጥታ ችግር በኦሮሚያና በትግራይ ተከስቷል፡፡ሁሉም አካላት ተጨማሪ የሰው ህይወት መጥፋት፣ መፈናቀልና አለመረጋጋትን እንዲቆሙ አሳስባለሁ“ ብለዋል ባችሌት፡፡
ባችሌት ”ሁሉም አካላት እውነትኛ፣ተዓማኒና አካታች የሆነ ንግግር” እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ኮሚሽነሯ የተጣለው የእንቅስቃሴ ገደብና የኢንተርኔት እንዲሁም የስልክ መቋረጥ እንደሚያሳስባቸውና መንግስት እንዲያስተካክል ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ባችሌት በኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች በአማራዎች ላይ ያደረሱት ጥቃት እንደሚያሳስባቸው ገልጸዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል በወቅቱ ግድያውን የሽብር ጥቃታ ያለው ሲሆን 32 ሰዎች መገደላቸውንም ቀደም ብሎ ያስታወቀ ሲሆን በዛሬው እለት ደግሞ ጥቃት የፈጸሙ 24 ታጣቂዎች መደምሰሳቸውን ገልጿል፡፡
ባችሌት ለኢትዮጵያ ድጋፍ እንደሚያደርጉና ኢትዮጵያም የሰብአዊ መብት በማክበር አካታች በሆነ መንገድ የማህበራዊና የኢኮኖሚ እድገት ታረጋግጣለች ብለዋል፡፡
የፌደሬሽን ምክርቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል ጣልቃ እንዲገባና ጊዜያዊ መንግስት እንዲቋቁም ውሳኔ አሳልፏል፡፡